የውጪ ምንዛሬ ገበያው ክፍት ከመደረጉ በፊት የሀገሪቱ የውጪ ምንዛሬ ግኝት እና ማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ስራ መሰራት እንዳለበት የአዲስ ቻምበር ጥናት ጠቆመ፡፡

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት መኖሩ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯልም ተባሏል፡፡

የውጭ ምንዛሬን ሙሉ በሙሉ ለገቢያው ክፍት ማድረግ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ውጤትን/ድብልቅ ውጤትን/ ሊያስከትል እንደሚችል ተነግሯል ፡፡

ይህ የተባለው የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባዛጋጀውና የውጭ ምንዛሬን ገቢያው እንዲወሰነው ክፍት ማድረግ እና የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን ይመሳላል በሚል በቀረበ ጥናት ላይ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የተለያዩ የንግዱ ማህበረሰብ ችግሮችን በጥናት ላይ በመመሰረት የአድቮኬሲ ስራ ይሰራል ፡፡

በጥናቱ ከውጭ ምንዛሬ ሰርዓቱ ጋር በተያየዘ ፅንሰ ሃሳቦች ምን ይላሉ ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ነፃ ያደረጉ የተለያዩ አገራት ተሞክሮ ምን ያሳያል ፣ አሁን ላይ በኢትዮጵያ ያለው የውጭ ምንዛሬ ሁኔታ ፣ ገቢያው ነፃ ሲደርግ በንግድ ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው ተዳሷል ፡፡

የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ ሊፈጠር የቻለበት የተለያዩ ምክንያቶች አንዳሉ የጠቀሱት ጥናት አቅራቢውና የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ኢያሱ ኩመራ የወጪ ንግድ አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን ፤ የሃብት ሽሽት ፣ የፖለቲካ አለመረጋጋት ፣ ጦርነት እና ሌሎችም ለምንዛሬው እጥረት አስተዋፆ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ፡፡

የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የብሄራዊ ባንክ አንዳንድ ህጎች ፣ የዋጋ ንረት እና ከውጭ ወደ አገር ውስጥ የሚላከው ገንዘብ በባንኮች በኩል አለመላክ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን እንዲባባስ ምክንያት መሆናቸውን አቶ እያሱ ኩመራ ጠቁመዋል፡፡

ታዲያ አሁን ላይ የሚታየውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ በእርግጥም የምንዛሬ ገቢያውን መክፍት አንዱ አማራጭ ሊሆን እንደሚችል አንስተዋል ፡፡

አቶ አያሱ አክለውም የተለያዩ አገራት የውጭ ምንዛሬ ገቢያቸውን ነፃ ማድረጋቸውን ጠቅሰው የአገራትን ተሞክሮ ለማሳየነት አቅርበዋል ፡፡

የምንዛሬ ገቢያውን ነፃ ያደረጉ አገራት የሚፍልጉትን ውጤት አስገኝተዋል ወይ የሚለውን በጥናታችን አይተናል ያሉት አቶ እያሱ አብዛኞቹ በማደግ ላይ ያሉ አገራት ያንን እውን ማድረግ አለመቻላቸውን ነው የገለፁት ፡፡

የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ነፃ ካደረጉ በኃላ አገራት የዋጋ ንረት ፣ የንግድ ሚዛን ጉድለት በመፍጠር የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት እንደገጠማቸው ጥናቶችን ዋቢ አድርገው ጠቅሰዋል ፡፡

እንደ ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰደው የኢስያ ሀገራት መሆኑን ጠቅሰው እነዚህ ሀገራት ውስን በሆነ ደረጃ ገቢያውን ከፍት ማድረጋቸው ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰዋል ፡፡

ሰኬታማ ሊሆኑ የቻለበት ምክንያት አንዱ ገቢያውን አንዴ ከመከፈት ይልቅ ቀስ በቀስ ( ግራጁሊዝም ) መንገድን መከተላቸው ፣ እወቀት መር መንገድን መከተላቸው ፣ ጠንካራ የማዕከላዊ ባንክ ያላቸው መሆኑ እና የትኛው መቅደም አለበት የሚለውን አካሄድ መከተላቸው ነው ብለዋል ፡፡

በአፍሪካም አስር የሚሆኑ አገራትን በተሞክሮ ለማሳየነት በጥናቱ መመልከታቸውን የጠቀሱት አቶ እያሱ ፤ እነዚህ አገራት የውጭ ምንዛሬውን ነፃ ከማድረጋቸው በፊት ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ገልፀዋል ፡፡

ሀገራቱ ከፍተኛ የሚባል የዋጋ ንረት ፣ የንግድ ሚዛን መዛባት ፣ የጥቁር ገቢያ መስፋፋት ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት በከፍተኛ ሁኔታ የወረደበትና መሰል ችግሮች ይስተዋል እንደነበረ ጠቅሰዋል ፡፡

በመሆኑም ይህንን ችግር ለመቅርፍ የውጭ ምንዛሬ ገቢያው እንዲመራው በሚል ነፃ ማድረጋቸው ድብልቅ የሆነ ነገር መፍጠሩን ጠቁመዋል ፡፡

መጀመሪያ አካባቢ ላይ ችግር እና አለመረጋጋት ቢኖርም በሂደት ወደ መረጋጋት መምጣቱን አመላክተዋል ፡፡

ሆኖም በቀጣይ የዋጋ እና የምንዛሬ መጠን መረጋጋት እንደመጣ ፣ የወጪና ገቢ ንግድ መጠንን እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ ክምችታቸውን ማሳደደግ ችለዋል ፡፡

የውጭ ምንዛሬ የገቢያ ሰርዓቱን ነፃ ያደረጉ ሀገራት መካከል የተሳካላቸው እንዳሉ ሁሉ ሰኬታማ ያልሆኑ አገራት መኖራቸውንም ጠቁመዋል ፡፡

ኬኒያ ፣ ዩጋንዳ መጀመሪያ አካበቢ ላይ ችግር ቢገጥመውም በሂደት መረጋጋት ችሏል ፡፡ ከኢሲያ ሀገራት መካከል ቻይና እና ደቡብ ኮሪያ ቀስ በቀስ ገቢያውን ነፃ ማድረጋቸው የተሳካ ገቢያን እንዲፈጠር እንዳስቻላቸው ተጠቅሷል ፡፡

ጋና እና ናይጀሪያ የውጭ ምንዛሬ ገበያን ነፃ ቢያደርጉም ውጤቱ ግን የሚፈለገውን አይነት አልነበረም ፡፡

በተለይ ናይጄሪያ የወጪ ንግዷ አነሰተኛ መሆንና የገቢ ምርት ላይ የተንጠለጠለች መሆኗ ውጤታማ መሆን አለመቻሉን ገልፀዋል ፡፡

ሱዳንም የውጭ ምንዛሬ ሰርዓቷን ገቢያ መር አድርጋው አምሳ አመት ብትሰራበትም ውጤታማ መሆን አለመቻሉን ተከትሎ እ. ኤ.አ በ1993 ነፃ መሆኑን አንሰታለች ፡፡ በአንፃሩ ሩሲያ እና ኡዝቤክስታን የውጭ ምንዛሬ ገበያቸውን በአንዴ ክፍት ማድረጋቸውን ተከትሎ ሰኬታማ መሆን እንደተሳናቸው አቅርበዋል ፡፡

ሌላኛው የጥናት አቅራቢ አቶ መላኩ ታንኩ በበኩላቸው በሀገሪቱ በመደበኛ ማለትም በባንክና በጥቁር ገበያ መካከል ልዩነት መስፋት አንደኛው ብሄራዊ ባንክ የሚቆጣጠረው መሆኑ ነው ብለዋል ፡፡

በተጨማሪም የውጪ ምንዛሬ በወረፋ እና በሰልፍ የሚገኝ በመሆኑ ፍላጎቱን ማሟላት እንዳልቻለ እና የጥቁር ገቢያውንም እያሰፋው እንደሆነ ጠቁመዋል ፡፡

ታዲያ የውጭ ምንዛሬውን ከመክፈታችን በፊት የዋጋ ንረት አሁን ካለበት መቀነስ ፣ የወጭ ንግድ ግኝታችንን ማሳደግ ፣ የክፍያ ሚዛን መስተካከል እና፣ የብሄራዊ ባንክ የቁጥጥር አቅም መጠናከር አለበት ብለዋል ፡

13 thoughts on “የውጪ ምንዛሬ ገበያው ክፍት ከመደረጉ በፊት የሀገሪቱ የውጪ ምንዛሬ ግኝት እና ማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ስራ መሰራት እንዳለበት የአዲስ ቻምበር ጥናት ጠቆመ፡፡

  1. hey there and thank you for your info – I’ve definitely picked up something new from right here.

    I did however expertise a few technical issues using this site, since I experienced to
    reload the site many times previous to I could get it to
    load properly. I had been wondering if your web host is OK?
    Not that I’m complaining, but slow loading instances times will often affect your placement in google and can damage your high-quality score if advertising and marketing with Adwords.
    Anyway I am adding this RSS to my e-mail and can look out for much
    more of your respective exciting content. Make sure you update this again very
    soon.. Escape roomy lista

  2. An impressive share! I’ve just forwarded this onto a co-worker who was doing a little research on this. And he actually ordered me dinner due to the fact that I discovered it for him… lol. So let me reword this…. Thank YOU for the meal!! But yeah, thanx for spending some time to discuss this topic here on your website.

  3. An impressive share! I have just forwarded this onto a coworker who had been conducting a little research on this. And he actually ordered me lunch because I stumbled upon it for him… lol. So allow me to reword this…. Thank YOU for the meal!! But yeah, thanx for spending the time to discuss this subject here on your web page.

  4. Having read this I thought it was really enlightening. I appreciate you spending some time and energy to put this content together. I once again find myself personally spending way too much time both reading and posting comments. But so what, it was still worth it.

  5. The very next time I read a blog, Hopefully it won’t fail me just as much as this one. I mean, Yes, it was my choice to read through, nonetheless I actually thought you’d have something helpful to talk about. All I hear is a bunch of complaining about something you could possibly fix if you were not too busy seeking attention.

  6. Next time I read a blog, Hopefully it doesn’t disappoint me as much as this particular one. I mean, Yes, it was my choice to read, nonetheless I genuinely believed you’d have something interesting to say. All I hear is a bunch of crying about something you can fix if you weren’t too busy looking for attention.

  7. Way cool! Some extremely valid points! I appreciate you penning this write-up and also the rest of the website is also really good.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *