ሁሉም የመንግሥትና የግል ባንኮች የትርፍ ምጣኔያቸው ይለያይ እንጂ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመትም በአትራፊነታቸው የቀጠሉ ሲሆን፣ የሀብት መጠናቸውን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግም በ2014 የሒሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ 2.3 ትሪሊዮን ብር አጠቃላይ ሀብት ማስመዝገብ ችለዋል። ባንኮቹ ያስመዘገቡት አጠቃላይ
የሀብት መጠን ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀርም በ21 በመቶ ብልጫ እንዳለው መረጃዎቹ ያመለክታሉ።
ሁሉም ባንኮች የሰበሰቡት የተቀማጭ ገንዘብ መጠንም በ2014 የሒሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ 1.6 ትሪሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው፡፡
