አዲስ ቻምበር የግሉን ዘርፍ በማጠናከር በሀገሪቱ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል።

አዲስ ቻምበር ከሚያከናውናቸው ስራዎች መካከልም የግሉን ዘርፍ አበይት ጉዳዮችን በማንሳት ሀገራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ማመቻቸት ነው።
እነዚህ የምክክር መድረኮች የግሉን ዘርፍና መንግስት ይበልጥ ተቀራርበው እንዲሰሩ ከማድረጋቸውም በላይ ጠንካራና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር የላቀ ሚና አላቸው።
የዚሁ አንድ አካል የሆነውና የውጪ ባንኮች በሀገራችን እንዲሰሩ መፈቀዱ ያለው እድልና ተግዳሮት / Opening of the Domestic Banking Sector to Foreign Banks: Opportunities and Challenges”. በሚል ርእስ ታላቅ የቢዝነስ ፓናል ውይይት አርብ ጥቅምት 18፣ ቀን 2015 ዓም ከ ጠዋቱ 2፡30 ሰአት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ተዘጋጅቷል፡፡
በመድረኩም ከመንግስት፣ከፋይናንስ ዘርፍ እና ከምሁራን የተለያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡