አዲስ ቻምበርና የኢፌዲሪ ፕላንና ልማት ሚንሰቴር በግሉ ዘርፍ ልማት ዙሪያ በጋራ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መከሩ ፡፡

አዲስ ቻምበርና የኢፌዲሪ ፕላንና ልማት ሚንሰቴር በግሉ ዘርፍ ልማት ዙሪያ በጋራ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መከሩ ፡፡
የአዲስ ቻምበር ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መሰንበት ሽንቁጤና ዋና ፀሃፊው አቶ ሺበሺ ቤተማርያም ከክብርት የፕላንና ልማት ሚንስትር ፍፁም አሰፋ ( ዶ/ር ) ጋር ተወያይተዋል፡፡
መንግስት በአስር ዓመቱ የልማት እቅድ ለግሉ ዘርፍ ትኩረት መሰጠቱን የጠቆሙት ዶ/ር ፍፁም ፤ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ ይበልጥ ተሳታፊ እንዲሆን ከአዲስ ቻምበር ጋር አብረን እንሰራለን ብለዋል ፡፡
ወ/ሮ መሰንበት ሽንቁጤ በበኩላቸው አዲስ ቻምበር በግሉ ዘርፍና በመንግስት መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር ድልድይ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል ፡፡
ሁለቱ ተቋማት በቀጣይ በግሉ ዘርፍ እድገት ላይና መሰል የኢኮኖሚ ልማት ዙሪያ በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡